| የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች | |
|
|
Author | Message |
---|
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Fri Aug 21, 2015 11:56 am | |
| አስራምስተኛዉ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ....መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት ---------------->------------------->እዚጋ የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት------------->
አስራ አምስተኛው የአለም አትሌትክስ ሻምፕዮና ዛሬ አርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ምሽት በድምቀት ይጀመራል፡፡ ውድድሩ ለቀጣዮቹ ዘጠኝ ቀናት ይቀጥላል፡፡ በዚህም ፎርም ኢትዮጵያ የምትሳተፍባቸውን ውድድሮች እና የውድድሩ ሰአቶች እንደዚሁም ውድድሩ የሚታይባቸውን ቻናሎች ዝርዝር ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ዉድድር በብዙ FTA ቻናሎች ስለሚተላለፍ የውድድሩን ሰአት ማወቅ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ይሆናል፡፡
ከመክፈቻው ስነስረአት ቀድሞ አንድ የፍፃሜ ዉድድር ይካሄዳል፡፡ የወንዶች ማራቶን! ኢትዮጵያ በዚህ ዉድድር በ ለሊሳ ደሲሳ ብርሀኑ ለሚ እና የማነ ፀጋይ ትሳተፋለች፡፡ ለሊሳ በዚህ አመት 2፡05፡52 የሆነ ሰአት አስመዝግቧል ፐርሰናል ቤስት ይሚባለው እና እስካሁን ከገባባቸው ሰአቶች ሁሉ ምርጡ ደግሞ 2፡04፡05 ነው፡፡ ብርሀኑ በዚህ አመት 2፡05፡28 የሆነ ሰአት አስመዝግቧል፡፡ ይህ ለራሱም ፐርሰናል ቤስት ተብሎ ተመዝግቦለታል፡፡ የየማነ በዚህ አመት ያስመዘገበው ምርጥ ሰአት በIAAF መዝገብ ላይ ባይሰፍርም አትሌቱ 2፡04:48 ፐርሰናል ቤስት እንዳለው ያሳያል፡፡ የውድድሩን መስፈርት አሟልተው ከቀረቡት ስልሳስምንት አትሌቶች ዉስጥ በፐርሰናል ቤስት ኬኒያውያኑ ላይ የሚደርስ አልተገኘም፡፡ ሁለት የኬኒያ ሯጮች 2፡02:57 እና 2፡03፡23 ፐርሰናል ቤስት ሰአት አስመዝግበዋል፡፡ በሲዝን ቤስት ደግሞ የኬኒያው አትሌት ኪፕሮቺ በ 2፡04፡47 ከቀረቡት ተወዳዳሪዎች መሃል ምርጡን የአመቱን ሰአት አስመዝግቧል፡፡ ብርሀኑ በ2፡05፡28 ከተወዳዳሪዎቹ መሀል ሁለተኛ ፈጣን ሰአት ይዟል፡፡ ባህሬን በ ሹሜ ደቻሳ፤ ስዊዘርላንድ ደግሞ በ ታደሰ አብርሐም ይሳተፋሉ፡፡ የዩጋንዳው ስቴፈን ኪፕሮቺም ግምት ከተሰጣቸው አትሌቶች ዉስጥ ይመደባል 2፡06፡33 አለው በዚህ አመት፡፡ ይህ ለሱ ፐርሰናል ቤስትም ጭምር ነው፡፡ እንግዴ ስለ አትሌቶቻችን ይህን ያክል ካልኩ ስለ ዉድድሩ ሰአት ልንገራችሁና አብረን በቴሌቪዝን መስኮት እንከታተል፡፡ ይህ የማራቶን ዉድድሩ አርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ከምሽቱ በስምንት ሰአት ከሰላስ አምስት (ምሽት 8:35) ላይ ይካሄዳል፡፡ ዉድድሩ ወደ ሁለት ሰአት ስለሚቆይ ሌሊት አስር ሰአት ብቅ ብላችሁም የመጨረሻውን 30 ደቂቃ መመልከት ትችላላችሁ፡፡ ጨለማው የቤጅንግን ከተማን እንደልብ እንዳንጎበኝ ሊያደርገን ነው ብላችሁም አትስጉ፤ እዛ ከጥሗቱ 1:35 ነው፡፡ ፀሐይ ወጣለች፡፡ ቻይና ቶሎ ነው የሚነጋው አይደል? መልካም ዕድል ለአትሌቶቻችን በመመኘት!
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ አገኙት? እንግዲያውስ በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
ab sat dish
Posts : 6 Points : 7 Reputation : 1 Join date : 2015-07-23 Age : 28 Location : Kolfe .tero &.Atenatera
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Fri Aug 21, 2015 1:19 pm | |
| | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Fri Aug 21, 2015 3:32 pm | |
| ውድድሩ በአገርዉስጥ ቻናሎች ይተላለፋል ተብሎ ይገመታል፡፡ በAD sport ባደር እና ናይል ላይ በFTA እንዲሁም በEurosport ዩቴልሳት@7E ላይ ውድድሩ ከሚተላለፍባቸው ቻናሎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ውድድሩን ከFTA ሳታላይት ቻናሎች በተጨማሪ በIAAF ኦፊሻል የYouTube ቻናል ጭምር LIVE መከታተል ይቻላል፡፡በ3ጂ ግን እንዳይሞክሩት፤በዋየርድ ብሮድባንድ ብቻ፡፡
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
PrinceHaire
Posts : 4 Points : 4 Reputation : 0 Join date : 2015-08-19
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Fri Aug 21, 2015 11:54 pm | |
| Bein sport 1 and 2 signal has down. Anybody any thought how i might gain control again on supermax SM9200 CA HD | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Fri Aug 21, 2015 11:57 pm | |
| - PrinceHaire wrote:
- Bein sport 1 and 2 signal has down. Anybody any thought how i might gain control again on supermax SM9200 CA HD
ለጥያቄህ መልስ ባይሆንም [You must be registered and logged in to see this link.] | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sat Aug 22, 2015 8:09 am | |
| ኢትዮጵያ በማራቶን ሁለተኛ፤ ሰባተኛ እና አስራአምስተኛ ሆና ዉድድሩን ጨርሳለች። የኤርትራው አትሌት ግርማይ ገብረስላሴ 2፡12፤28 በሆነ ሰአት ወርቅ ሲያገኝ፤ የማነ በአርባ ሰከንድ ልዩነት ተከትሎት ገብቷል፡፡ የዩጋንዳው ሙታይ ደግሞ ሶስተኛ ሆኖ ዉድደሩን አጠናቋል፡፡
ውድድሩን ከጀመሩት ስልሳስምንት አትሌቶች ውስጥ አርባ ሁለቱ ውድድርን መጨረስ ሲችሉ፤ ሃያስድስቱ ግን ሳይጨርሱ አቆርጠዋል፡፡ ውድድሩን ከጨረሱት ውስጥ የታንዛኒያው ፋቢያኖ ጆሴፍ በ2፡35:27 በአርባሁለተኛነት ሲገባ ለራሱ የአመቱን ምርጥ ሰአት በማስመዝገብ ጭምር ነበር፡፡ አንድ የኬኒያ አትሌት ሃያሁለተኛ በመሆን ሲጨርስ የተቀሩት ሁለቱ ግን አቅርጠው ወጠዋል፡፡
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sat Aug 22, 2015 10:20 am | |
| ዛሬ ከሰአት በኋላ በ9:50 ላይ የወንዶች 10,000m የፍፃሜ ዉድድር
ኢትዮጵያ በኢማነ መርጊያ፣ሙክታር እድሪስ እና ሞሲነት ገረመው ለውድድር ተዘጋጅታለች፡፡ በዚህ ዉድድር ላይ ከሚካፈሉ ሯጮች ሁሉ የአመቱ ምርጥ ሰአት ያለው፤ ለብሪታንያ የሚሮጠው ሞፋራህ ነው፡፡ ከተሰላፊዎቹ ዉስጥ ኬንያዊው ፖል ታንዋይ እና ሞፋራህ በዚህ አመት ከ27ደቂቃ በታች መግባት የቻሉ ብቸኛዎቹ ናቸው፡፡
አሜሪካዊው ጋለን ሩፕ በዚህ ውድድር ተካፋይ ነው፡፡ በዝህ አመት ጥሩ የሚባል ሰአት አላስመዘገበም፡፡ ይልቅን ለካናዳ የሚሮጠው ካሜሮን ሌቪንስ በያዝነው አመት ጥሩ ሰአት ካስመዘገቡት ዉስጥ ተጠቃሽ ነው፡፡ ባህሬን አውቀ አያሌውን አሰልፋለች፡፡
እስካሁን በተደረገው ዉድድር(አንድ ብቻ ነው) የሜዳልያ ሰንጠረዡን የአፍሪካ ሃገራት ከአንድ እስከ ሶስት ይዘዉታል፡፡ ኤርትራ፤ ኢትዮጵያና ዩጋንዳ በመከታተል፡፡ ይህ የደረጃ ሰንጠረዥ የወንዶች አስርሺ ፍፃሜ እስከሚደረግ ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል፡፡ መልካም እድልን እንመኛለን!
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ አገኙት? እንግዲያውስ በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sun Aug 23, 2015 2:15 am | |
| የሜዳልያ ሰንጠረዥ ERITREA ..............1ወርቅ GREAT BRITAIN & N.I...1ወርቅ GERMANY...............1ወርቅ KENYA.................1ብር+1ነሐስ PR OF CHINA1..........1ብር ETHIOPIA..............1ብር UGANDA................1ነሐስ UNITED STATES.........1ነሐስ
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Tue Aug 25, 2015 10:24 am | |
| እስካሁን ባለው ሂደት ጎረቤት አገር ኬኒያ በ 2ወርቅ፤2ብር እና 2ነሃስ የደረጃ ሰንጠረዡን በአንደኝነት ትመራለች፡፡ እኛም ብሩ ካለ ወርቁ ከገቢያ ብለን በ 2ብር ከአስትናጋጇ ቻይና ጋር በ11ኛ ደርጃ ላይ እንገኛለን፡፡ እስካሁን 19አገሮች መዳሊያ ማግኘት ችለዋል፡፡
የወንዶች 800ሜትር ፍጻሜ ዛሬ ከቀኑ 9:55 ላይ ይደረጋል ኬኒያውያኖቹ በዚህም ሌላ ወርቅ አምጥተው መሪነታችውን አጠናክረው እንደሚይዙት ባለሙሉ ተስፋናቸው፡፡ ባይታገድ ኖሮ መሃመድ አማን ይህን ተስፋቸውን ፉርሽ ሊያደርገው ይችላል ተብለው ከሚጠበቁት አትሌቶች ዉስጥ ነበር፡፡
የሴቶች 1500ሜትር ፍፃሜ ዛሬ ከቀኑ 9:35 ላይ ይደረጋል የቀድሞ ሻምፒዮና የስዊድን አትሌት አበባ አረጋዊ የምትሳተፍበትን ይህን ዉድድር ከኢትዮጵያዊቷ ገንዘቤ ዲባባ ላይ እንዲህ በቀላሉ የሚወስድ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ ኬኒያውያኑ ግን በFaith Chepngetich Kipyegon አሁንም ሌላ ፈተና ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ይፈራል፡፡
ለአትሌቶቻችን መልካሙን ሁሉ በመመኘት!
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Tue Aug 25, 2015 4:18 pm | |
| ኬኒያውያኖቹ የ400 መሰናክልና የ800ሜትር ወርቀን ወስደዋል፡፡ መሪነታቸውንም ይበልጥ አጠናክረውታል፡፡ ገንዘቤም እንደተገመተው 1500ን አላስቀምስ ብላለች፡፡የመጀመርያውን ወርቅ ላገሯ በማስገኘት።
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Wed Aug 26, 2015 12:08 pm | |
| እስካሁን አስራስምንት የፍጻሜ ውድድሮች ተካሂደዋል ከተበረከቱት አስራስምንት የወርቅ ሜዳሊያ ዉስጥ ኬኒያ፣ ብሪታኒያ እና ጀማይካ፤ አራት ሶስት ሁለት በድምሩ ዘጥኝ ወርቅ በማግኘት የወርቅ ሜዳልያውን ሃምሳ ፐርሰንት በእጃቸው አስገብተዋል፡፡
የዉድሩ መሪ ኬኒያ እስካሁን ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን አግኝታለች፡፡ አራት የዋርቅ፣ ሶስት የብር እና ሁለት የነሀስ፡፡ ኢትዮጵያ በአንድ ወርቅና ሁለት ነሃስ ደረጃዋን ወደ አምስት ከፍ አድርጋለች፡፡
እስከአሁን ሃያአምስት አገራት ሜዳልያ ማግኘት ችለዋል፡፡ ዛሬ እኛ የምንካፈልበት የፍፃሜ ዉድድር አይኖርም ኬኒያውያን ሴቶች ግን ሶስት ሺ መሰናክል ፍፃሜን በጉጉት ይጠባበቅሉ፡፡ ለአፍሪካውያኑ መልካም እድል እንመኛለን፡፡
የወንዶች የአምስትሺሜትር ማጣርያን ሁሉም ኢትዮጵያውያን አልፈዋል፡፡ ዮሚፍ ቀጀልቻ ሞፋራህን አስከትሎ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፤ ሓጎስ ገብረሕይወት እና ኢማነ መርጊያ ደግሞ በሌላ ምድብ አንደኛና አምስተኛ በመሆነ ለፍፃሜ አልፈዋል፡፡ ሞፋራህ የነበረበት እና ዮሚፍ በአሸናፊነት ያጠናቀቀበት ምድብ ፈጣን ሰአት የተመዘገበበት ሲሆን የገቡበት ሰአት ከመጀመሪያው ምድብ ከ25ሰከንድ በላይ የተሻለ ነበር፡፡ የዚህ ዉድድር ፍፃሜ ቅዳሜ በ ስምንት ሰአት ተኩል የሚካሄድ ይሆናል፡፡ መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Wed Aug 26, 2015 4:58 pm | |
| ኬኒያ በስድስት ወርቅ አንደኝነቷን አጠናክራለች የኋላ ኋላ አንደኝነቷን ለሃያላኑ አገራት አሳልፋ ትሰጣለች ተብሎ ቢገመትም ኬኒያውያኑ ግን አንደኛ ሆኖ ለመጨረስ ቆርጠው መነሳታቸውን አሳይተዋል፡፡ ከትራክ ዉድድር አልፈው የፊልድ ዉድድርንም ወርቅ ወደራሳቸው ካዝና መክተት ጀምረዋል፡፡
የጦር ዉርወራን በወንዶች ወርቅ ወስደዋል፡፡ የሚጠብቁትን ሌላ ወርቅም በትራክ ዉድድር በሴቶች ሶስት ሺ መሰናክል አግኝተዋል፡፡ ብሪታንያ በሶስት ወርቅ ሁለተኛ ናት፡፡ ዩናይተድ ስቴትስ እና ጀርመን አሁንም አንድ ወርቅ ብቻ ነው ያላቸው፡፡
አዝጋጁዋ ቻይና ወርቅ ነጥፎባታል፤ ሁለት ብር እና ነሃስ ነው እስካሁን ያገኘችው፡፡ አሁን ኬኒይያዊያኖቹ ላይ ሊደርሱ ይችላሉ ተብለው የሚገመቱት የአጭር እርቀት ተወርዋሪዎቹ ጀማይካዊያን እና ሶስት ወርቅ ያላት ብሪታንያ ናት፡፡ ሆኖም ኬኒያ ዙሩን የምር አክርራዋለች፡፡
ለአፍሪካ አዲስ ሪከርድ ይዛም ልትጨርስ ነው፡፡ ካሁን በኋላ በቀሪዎቹ የሴቶች እና የወንዶች 5ሺን ካልጨመሩ፤ እስካሁን ኬኒያውያን ከኛ ላይ የወስዱት የሴቶችን የ10ሺ ሜትር ወርቅ ብቻ ነው፡፡ ጎረቤት ኬኒያን እያስመዘገበች ባለችው ዉጤት እንኩዋን ደስ አለሽ ማለት እንወዳለን፡፡
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Thu Aug 27, 2015 9:13 am | |
| የዛሬዉን የቤጂንግ ዉድድር በዩቴልሳት@7.0°E ፊድቻናል 11080 H 9874(24 0C 95 C5 4F EC 63 9E) ላይ መከታተል ይቻላል፡፡
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sat Aug 29, 2015 12:55 am | |
| የውንዶች አምስት ሺ የፍፃሜ ዉድድር ዛሬ በ 8:30ኢትዮጵያ በ ሶስት አትሌቶች ትወከላለች ፡-
- Yomif Kejelcha
- Hagos Gebrhiwet
- Imane Merga
Mo Farah ትልቅ ግምት ተሰጦታል፡፡ ኬኒያም እንደኛው በሶስት አትሌቶች ትወከላለች፡፡ USA ወርቋን አራት አድርሳለች፡፡ በሴቶችም በወንዶችም አራት በመቶና አራት በአራት መቶ የዱላ ቅብብል ዉድድሮች ላይእንደምታይል ከወዲሁ ተገምቷል፡፡ እናም ኬኒያ አንደኝነትዋን አስጠብቃ ለመጨረስ ዛሬ የሚደረገውን የወንዶችስምንት መቶ ሜትር ፍጻሜ ዉድድር በጉጉት ትጠብቃለች፡፡ መልካም እድል! መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sat Aug 29, 2015 3:50 pm | |
| ሞ ፋራህ ወርቁን በድጋሚ በ አምስትሺም ወስዷል። ኬኒያና ኢትዮጵያ ሁለትኛና ሶስተኛ ሆነው ጨርሰዋል፡፡ USA አምስተኛ ወርቋን አግኝታለች፡፡ አንደኛ ሆና መጨረሷም አይቀሬ እየሆነ ነው፡፡ የሴቶች ስምንት መቶ ሜትሩን ኬኒያ አልቀናትም፤ ሶስተኛ ሆና ነው የጨረሰችው፡፡ አሁን ለኬኒያም ሆነ ለኢትዮጵያ የሚጠበቀው የነገው የሴቶች አምስትሺ እና ማራቶን ነው፡፡ የወንዶች ሺአምስትመቶም ነገ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sat Aug 29, 2015 6:45 pm | |
| ወቅታዊው የሜዳሊያ ሠንጠረዥደረጃ | ሀገር | ወርቅ | ብር | ነሐስ | ድምር |
|
|
|
|
|
| 1 | ኬኒያ | 6 | 4 | 3 | 13 |
|
|
|
|
|
| 2 | ጀማይካ | 6 | 2 | 3 | 11 |
|
|
|
|
|
| 3 | አሜሪካ | 5 | 5 | 6 | 16 |
|
|
|
|
|
| 4 | ብሪታኒያ | 4 | 1 | 0 | 5 |
|
|
|
|
|
| 5 | ፖላንድ | 3 | 1 | 4 | 8 |
|
|
|
|
|
| 6 | ሩሲያ | 2 | 1 | 1 | 4 |
|
|
|
|
|
| 7 | ኪዩባ | 2 | 1 | 0 | 3 |
|
|
|
|
|
| 8 | ቻይና | 1 | 5 | 1 | 7 |
|
|
|
|
|
| 9a | ካናዳ | 1 | 3 | 3 | 7 |
|
|
|
|
|
| 9b | ጀርመን | 1 | 3 | 3 | 7 |
|
|
|
|
|
| 11 | ኢትዮጵያ ሀገራችን | 1 | 2 | 1 | 4 |
|
|
|
|
|
|
ጀማይካዎቹ በዱላ ቅብብል በወንዶቹም በሴቶቹም 4x100ን እየተወረወሩ ወርቁን ወስደዉታል፡፡ የመቶ ሜትሮቹ ባለወርቅ ሁሴን ቦልት እና ፍሬይዘር ፕሪስ ዱላዉን ይዘው ሌላ ወርቅ በጋራ አምጥተዋል፡፡ አሁን ጀማይካም ከኬኒያ እኩል ስድስት ወርቅ አላት፡፡ አንዱን ወርቅ USA አግኝታው ቢሆነ ኖር መሪነቱን ትረከብ ነበር። መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sun Aug 30, 2015 5:26 am | |
| ማሬ ዲባባ በሴቶች ማራቶን አሸናፊ ሆናለች። ለ ኢትዮጵያም ሁለተኛው ወርቅ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sun Aug 30, 2015 2:17 pm | |
| Happening now 5,000m final | |
|
| |
kstar Senior member
Posts : 1052 Points : 2020 Reputation : 842 Join date : 2015-05-23
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች Sun Aug 30, 2015 7:23 pm | |
| ዛሬ የቤጅንግ የአለም ሻምፒዮና ፍጻሜ አግኝቷል የሜዳሊያ ሠንጠረዡም እንደሚከተለው ነውደረጃ---- | ሀገር-------------- | ወርቅ--------- | ብር---------- | ነሐስ---------- | ድምር--------- |
|
|
|
|
|
| 1 | ኬኒያ | 7 | 6 | 3 | 16 |
|
|
|
|
|
| 2 | ጀማይካ | 7 | 2 | 3 | 12 |
|
|
|
|
|
| 3 | አሜሪካ | 6 | 6 | 6 | 18 |
|
|
|
|
|
| 4 | ብሪታኒያ | 4 | 1 | 2 | 7 |
|
|
|
|
|
| 5 | ኢትዮጵያ | 3 | 3 | 2 | 8 |
|
|
|
|
|
| 6 | ፖላንድ | 3 | 1 | 4 | 8 |
|
|
|
|
|
| 7a | ካናዳ | 2 | 3 | 3 | 8 |
|
|
|
|
|
| 7b | ጀርመን | 2 | 3 | 3 | 8 |
|
|
|
|
|
| 9 | ሩሲያ | 2 | 1 | 1 | 4 |
|
|
|
|
|
| 10 | ኪዩባ | 2 | 1 | 0 | 3 |
|
|
|
|
|
| 11 | ቻይና | 1 | 7 | 1 | 9 |
|
|
|
|
|
| መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ሲያገኙት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያርጉት፡፡ | |
|
| |
Sponsored content
| Subject: Re: የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች | |
| |
|
| |
| የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ፕሮግራሞች | |
|